‘ሁከት ይወገድልኝ’ – የሰበር ችሎት የህግ ትርጉም BY ABRHAM YOHANNES ON NOVEMBER 20, 2017


የአንድ ንብረት ባለይዞታ የሆነ ሰው ይዞታውን ለመንጠቅ ወይም በይዞታው ላይ ሁከት ለመፍጠር የሚፈፀምን ማንኛውንም ድርጊት እንዲቆም ወይም ንብረቱ እንዲመለስለት የሚያቀርበው የይዞታ ክስ

በፍ/ሕ/ቁ. 1149/1/ መሰረት የሁከት ይወገድልኝ ክስ መቅረብ የሚችለው አቤቱታ አቅራቢው ለክርክሩ መነሻ በሆነው ነገር በቀጥታ ወይም በጠባቂ ይዞታ ሲኖረው ነው፡፡ እንዲሁም የይዞታ ክስ የሚቀርበው ለክርክሩ መነሻ የሆነውን ንብረት በወቅቱ ለመያዝ ምንም ዓይነት መብት በሌለው ሰው ላይ ስለመሆኑም የድንጋጌው መንፈስ ያስረዳል፡፡ የሁከት ይወገድልኝ አቤቱታ አቅራቢ በማስረጃ ማረጋገጥ ያለበት ንብረቱ በይዞታው ስር የነበረና የሁከት ድርጊት ፈፃሚው የኃይል ተግባር በመጠቀም ወይም በሚስጢር ንብረቱን የወሰደበት መሆኑን ነው፡፡ ሁከት ተፈጥሯል የሚባለው ባለይዞታ የሆነው ሰው በይዞታው ስር በሚገኘው ንብረት እንዳይገለገልበት ሌላ ሰው ጣልቃ ገብቶበት መሰናክል ሲፈጥርበት ወይም ረብሻ ሲፈጥርበት ነው፡፡

ሰ/መ/ቁ. 80241 ቅጽ 15፣[1] ፍ/ህ/ቁ. 1149(1)

የሁከት ይወገድልኝ ክስ ለማቅረብ ከሳሹ ማስረዳት ያለበት ባለቤትነት ወይም የባለቤትነት ማረጋገጫ ሰርተፊኬት እንዳለው ሳይሆን ክስ ያቀረበበት ንብረት ህጋዊ ባለይዞታ መሆኑ በሌላ አነጋገር ሁከት የተፈጠረበትን ነገር በእጁ አድርጎ በእውነት ሲያዝበት እንደነበር ነው፡፡

ሰ/መ/ቁ. 38228 ቅጽ 9[2]

ሁከት እንዲወገድ በቀረበ ክስ ተከሳሽ የሚያነሳው የባለቤትነት ክርክር እራሱን የቻለ ባለቤትነት የመፋለም ክስ /petitory action/ በሚመለከተው ላይ አቅርቦ ከሚታይ በስተቀር ሁከት ተፈጥሯል ወይስ አልተፈጠረም ተብሎ ለሚያዘው ጭብጥ ተገቢነት የለውም፡፡

ሰ/መ/ቁ. 27506 ቅጽ 6[3]

የሁከት ይወገድልኝ ክስ ሲቀርብ በፍርድ ቤት በጭብጥነት ተይዞ መፈታት የሚገባው ጉዳይ ሁከት አለ ወይንስ የለም? የሚለው ነው፡፡

የውሉ ተገቢውን የአጻጻፍ ሥርዓት ተከትሎ አለመደረግ ይዞታው በተጨበረበረ መንገድ ስለመያዙ ወይንም በማናቸውም ሕገወጥ ሁኔታ ስለመያዙና ሁከት እንዲወገድለት ክስ ያቀረበው ከሳሽ በይዞታው በእውነት ሊያዝበት እንደማይችል አያረጋግጥም፡፡ በዚህ ረገድ ውሉ ጉድለት አለበት ከተባለ በፍ/ብ/ሕ/ቁ/1808(2) ላይ እንደተመለከተው ውሉ ፈራሽ ነው እንዲባል የክስ ምክንያት ከሚሆን በስተቀር ሁከት ይወገድልኝ ተብሎ በቀረበ ክስ ላይ ሊስተናገድ የሚችል አይሆንም፡፡

ሰ/መ/ቁ 36645 ቅጽ 9[4]

በአብላጭ ድምፅ የተሰጠ

[1] አመልካች ጽናት የሆቴል ቱሪዝም ስራዎች ኃ.የተ. የግል ማህበር እና ተጠሪ አቶ ዳመነ ነጋ /5 ሰዎች/ የካቲት 12 ቀን 2005 ዓ.ም.

[2] አመልካች ሐጂ መሀመድ አወል ረጃ እና ተጠሪ እነ አቶ ዲኖ በሺር /2 ሰዎች/ ታህሣሥ 7 ቀን 2001 ዓ.ም.

[3] አመልካች እነ ሣሙኤል ውብሸት እና ተጠሪ ብዙነህ በላይነህ ሐምሌ 19 ቀን 1999 ዓ.ም.

[4] አመልካች ረዳት ሳጂን አያኖ አንጀል እና ተጠሪ እነ ወ/ሮ ዓሇሚቱ ህዳር 11 ቀን 

Advertisement

በአገራችን የአስተዳደራዊ ድንጋጌ አወጣጥ ላይ የሚስተዋሉ የቋንቋ፣ የህትመት እና ተያያዥ ችግሮች BY ABRHAM YOHANNES ON NOVEMBER 21, 2017


በህግ አውጭው የወጣ አንድ አዋጅ ስጋና ደም ለብሶ በተጨባጭ ተፈጻሚነት እንዲያገኝ ብዙውን ጊዜ ዝርዝር የአፈጻጸም መመሪያዎች ያስፈልጉታል፡፡ በኢትዮጵያ ያለውን ሁኔታ ያየን እንደሆነ አንድ የመንግስት ሰራተኛ በተወካዮች ም/ቤት ከሚወጣው አዋጅ ይልቅ በየጊዜው ስለሚደነገጉት መመሪያዎች የተለየ ቅርበትና እውቀት አለው፡፡ በእያንዳንዱ አስተዳደር መ/ቤት ውስጥ የመንግስት ስራ የሚሰራው ‘በህጉ መሰረት’ ሳይሆን ‘በመመሪያው መሰረት’ ስለመሆኑ እውነትነት ያለው ሀቅ ነው፡፡

ስልጣን በሰጠው አዋጅ መሰረት እስከወጣ ድረስ በመመሪያ መስራቱ ባልከፋ ነበር፡፡ ሆኖም ኢትዮጵያ ውስጥ ‘መመሪያ’ ሲባል ከስልጣን በላይ ለሆነ ድርጊት፣ ለህገ ወጥነትና ለኢ-ፍትሐዊነት የሚሰጥ የሽፋን ልብስ ነው፡፡ ዋና ችግሩ ከውክልና ሰጪው ከተወካዮች ም/ቤት ይጀምራል፡፡ በተለያዩ አዋጆች ላይ ለሚኒስትሮች ም/ቤትና ለአስተዳደር መ/ቤቶች በውክልና የሚተላለፈው ስልጣን እንደሰማይ የሰፋ ቢሆንም ጥያቄው የህግ የበላይነትና የህገ-መንግስታዊነት ሆኖ ተመክሮበት አያውቅም፡፡

ከዚህ ባሻገር አነስተኛ ስነ-ስርዓት ፈጽሞ አለመኖሩ መመሪያዎች ‘የስርቻው ስር ህጎች’ ሆነው እንዲቀሩ አድርጐታል፡፡ በተጨማሪም ህጋዊነታቸውንና በህግ አውጭው ከተሰጣቸው ስልጣን በላይ አለማለፋቸውን በተግባር የሚያረጋግጥ ውጤታማ የቁጥጥር ስልት አልተዘረጋም፡፡

     መመሪያ የሌለው መመሪያ

አስተዳደራዊ ድንጋጌ አወጣጥ ስርዓት (Rule–Making Procedure) ግልፅነትና የህዝብ ተሳትፎን በማሳካት ረገድ ካለው ወሳኝ ሚና በተጨማሪ በዘፈቀደ በሚወጡ ደንብና መመሪያዎች አማካይነት የዜጐች መብትና ነፃነት እንዳይጣስ ከለላና ውጤታማ የመቆጣጠሪያ መሳሪያ ነው፡፡ በአገራችን በሚኒስትሮች ም/ቤትና በአስተዳደር መ/ቤቶች የሚወጡ ደንቦችና መመሪያዎች ለየትኛውም አይነት አስገዳጅ ስነ-ስርዓት አይገዙም፡፡ እስከ አሁን ድረስ ህግ አውጭው አንድ ደንብ በሚኒስትሮች ም/ቤት የሚወጣበትን ስነ-ስርዓት በአዋጅ ደንግጐ አላስቀመጠም፡፡ በተመሳሳይ መልኩ የአስተዳደር መ/ቤቶች መመሪያ ሲያወጡ ሊከተሉት ስለሚገባ ስነ-ስርዓት የሚደነግግ አስገዳጅ ህግ የለም፡፡

ከመሰረታዊ የስነ-ስርዓት ቅድመ ሁኔታዎች አንዱና ዋነኛው አስተዳደራዊ ድንጋጌ ቀላል በሆነ መንገድ ታትሞ መሰራጨት ያለበት መሆኑ ነው፡፡ በተግባር ያለው እውነታ እንደሚያሳየን መመሪያዎች በአስተዳደር መ/ቤቱ ውስጥ ተደብቀው የሚቀሩ የጓዳ ህጐች ናቸው፡፡ አብዛኛዎቹ መመሪያዎች በ3ኛ ወገን ላይ አስገዳጅነት ቢኖራቸውም ሊታወቁና ሊከበሩ የሚችሉበት አንዳችም አማራጭ መንገድ የለም፡፡ ግለሰቦች እና ድርጅቶች በመመሪያው መሰረት እርምጃና ቅጣት ሲወሰድባቸው መመሪያዎቹ ባልታወቁበትና ባልታተሙበት ሁኔታ ነው፡፡ ይህም የግልፅነትን መርህ የሚጥስ፣ ለሙስናና ከስልጣን በላይ ለሆነ ድርጊት እና በስልጣን አለአግባብ መገልገል በአጠቃላይ ለአስተዳደራዊ ብልሹነት የሚያጋልጥ አደገኛ ሁኔታ ነው፡፡ ማንም ዜጋ ላልታተመ፣ ለማያውቀው እና ሊያውቀው ለማይችል ህግ የመገዛት ግዴታ የለበትም፡፡

የመመሪያዎች አለመታተም ተፈጻሚነት (ውጤት) የሚያገኙበትን ጊዜ ለመወሰን አስቸጋሪ ያደርገዋል፡፡ ለመሆኑ አንድ መመሪያ ውጤት የሚኖረው ከመቼ ጀምሮ ነው? በተለምዶ በመ/ቤቱ ኃላፊ ከተፈረመበት ቀን ጀምሮ ውጤት ያገኛል፡፡ ሆኖም አንዳንድ ጊዜ ያልተፈረመ መመሪያ በተግባር ተፈጻሚ የሚደረግበት ሁኔታ ያጋጥማል፡፡ በአንዳንድ መመሪያዎች ላይ ደግሞ ተፈጻሚ የሚሆንበት ቀን በግልጽ ቢመለከትም የመ/ቤቱ ኃላፊ ፊርማ የለውም፡፡

በስነ-ስርዓት አለመኖር ምክንያት በየአስተዳደር መ/ቤቱ የሚወጡት መመሪያዎች ቅርጽና ይዘት ወጥነት አጥቷል፡፡ መመሪያ ለአውጭውም አካል ሳይቀር አስገዳጅ ህግ እንደመሆኑ አነስተኛ የሚባሉ ቅድመ ሁኔታዎች ሊሟሉ ይገባል፡፡ ለምሳሌ የመመሪያው መለያ ቁጥር፣ የተሻረ መመሪያ ካለ ቁጥሩና የወጣበት ጊዜ አንዲሁም ስልጣን የሰጠውን አዋጅ ቁጥርና አንቀጽ መጥቀስ ይገባል፡፡ እንዲሁም መመሪያው በምእራፍ፣ በክፍልና በአንቀጽ (ቁጥር) ተከፋፍሎ አስገዳጅነት ያለው ድንጋጌ ሊያስቀምጥ ይገባል፡፡ ይዘቱ ጥናት፣ ጥቆማ ወይም ምክር ወዘተ… መምሰል የለበትም፡፡

ህትመትና የሰበር ችሎት አቋም

መመሪያዎች በይፋ አለመታተማቸው በፍትሐብሔር እና የወንጀል ክርክሮች የሚረጋገጡበትን መንገድ ያወሳስበዋል፡፡ አውጭው አካል በተከራካሪነት ሲሰለፍ መመሪያ ጠቅሶ የሚያቀርበው ክርክር መመሪያውን እንደ አንድ የማስረጃ ዓይነት ለፍርድ ቤቱ በማቅረብ መደገፍ ይኖርበታል፡፡ ምክንያቱም ከእርሱ በስተቀር ፍርድ ቤቱ ሆነ ባለጋራው ተከራካሪ ስለመኖሩ ሊያውቁ አይችሉም፡፡ ስራ ላይ መዋሉ ሊታወቅና ሊረጋገጥ የሚችለው የተባለውን መመሪያ እንዳወጣ የሚከራከረው የመንግስት ተቋም እንደ ሰነድ ማስረጃ ከመዝገቡ ጋር ማያያዝ ሲችል ነው፡፡

አስቸጋሪ ሁኔታ የሚፈጠረው መመሪያውን ያወጣው አካል ተሳታፊ በማይሆንባቸው ክርክሮች ይዘቱ በአንደኛው ወገን መከራከሪያ ሆኖ ሲቀርብ ነው፡፡ ለምሳሌ ይህ ተከራካሪ ትክክለኛውን የመመሪያ ቁጥር መለየት ሳይችል ሲቀርና መኖሩ በተቃራኒ ወገን ሲካድ ፍርድ ቤቱ ሊከተለው የሚገባው አቅጣጫ ምንድነው? በመመሪያው መኖር ተጠቃሚነቱን ገልጾ የሚከራከረው ወገን የማስረዳት ግዴታውን ስላልተወጣ ክርክሩን ውድቅ ማድረግ አንደኛው አማራጭ ነው፡፡ ሆኖም ይህ አካሄድ ፍትሐዊነት ይጎድለዋል፡፡ መሰረታዊ የማስረጃ ህግ ደንቦችንም አያሟላም፡፡ አንድ ተከራካሪ አስገዳጅነት ያለውን የህግ ድንጋጌ ጠቅሶ ከመከራከር ባለፈ ‘ህግ እንደማስረጃ’ እንዲያቀርብ አይገደድም፡፡

‘መመሪያ ህግ ነው’ እስከተባለ ድረስ ካለበት ቦታ ማስቀረብ ዞሮ ዞሮ ፍርድ ቤቱ ጫንቃ ላይ ያርፋል፡፡ ሆኖም ያልታተመ መመሪያ ፍርድ ቤቶች ግንዛቤ እንዲወስዱበት አይገደዱም፡፡ ከዚህ በተቃራኒ የሰበር ችሎት በሰ/መ/ቁ. 40804[1] በሰጠው የህግ ትርጉም፤

…በመንግስት የሚወጡ ሕጏች እና መመሪያዎች፣ ደንቦች፣ ወዘተ በግልጽ የሚታወቁ እንደመሆናቸው ፍ/ቤቶች (ዳኞች) ግንዛቤ የሚወስዱባቸው ናቸው፡፡

ችሎቱ ያንጸባረቀው አቋም ዳኞች ያልተጻፈ እንዲያነቡ የማስገደድ ያክል ነው፡፡ እንደ ችሎቱ ከሆነ መመሪያ-ጠቀስ ክርክር በተከራካሪ ወገኖች ባይቀርብም ለውሳኔ አሰጣጥ የሚረዳ መመሪያ ካለ ፍርድ ቤቱ መኖሩን ማወቅ አለበት (በይግባኝ ደረጃ ደግሞ ማወቅ ነበረበት) ማለት ነው፡፡

የነጋሪት ጋዜጣ አዋጅ ዳኞች ያልታተሙ መመሪያዎችን ግንዛቤ እንዲወስዱባቸው አያስገድድም፡፡ የፌደራል ነጋሪት ጋዜጣ ማቋቋሚያ አዋጅ ቁ. 3/1987 አንቀጽ 2/3/ ህግ ተርጓሚውን ጨምሮ ማናቸውም የፌደራልና የክልል የመንግስት አካላት እንዲሁም ህጋዊ ሰውነት ያገኘ ማንኛውም ድርጅት በነጋሪት ጋዜጣ የሚወጣን ህግ የመቀበል ግዴታ (shall take judicial notice of Laws published in the Federal Negarit Gazeta) አለበት፡፡ ስለሆነም ችሎቱ በሰ/መ/ቁ. 40804 ያንጸባረቀው አቋም ከነጋሪት ጋዜጣ ህጉ ጋር አይስማማም፡፡

ችሎቱ በከፊል የተለሳለሰ አቋም የያዘው በሰ/መ/ቁ. 83060[2] ሲሆን በመዝገቡ በሰፈረው የህግ ትርጉም መሰረት ክርክር የቀረበበት መመሪያ ይዘት ለውሳኔ አሰጣጥ አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝ ፍርድ ቤት በፍ/ስ/ስ/ህ/ቁ. 145(1) እና 345(1)(ለ) ማስቀረብ ይገባዋል፡፡ ይህም ማለት አንደኛው ተከራካሪ መመሪያ ጠቅሶ ካልተከራከረ ወይም የመዝገቡ አካል እንዲሆን ካላሳሰበ በስተቀር የማስቀረብ ግዴታ አይኖርም፡፡ ፍርድ ቤትም በዚህ መልኩ ያልተነሳን ወይም በክርክሩ ያልተጠቀሰን መመሪያ በውሳኔው ከግምት ውስጥ ባለማስገባቱ ብቻ ውሳኔው በህግ ስህተት በይግባኝ ወይም በሰበር ሊሻር አይገባውም፡፡

የነጋሪት ጋዜጣ የህትመት ቅድመ ሁኔታ

ለመመሪያዎች አለመታተም ዋናው ምክንያት ልማድ እንጂ ህግ አይደለም፡፡ የፌደራል ነጋሪት ጋዜጣን ለማቋቋም የወጣው አዋጅ ማናቸውም የፌደራልመንግስት ህግ በነጋሪት ጋዜጣ እንዲወጣ ያስገድዳል፡፡[3] አዋጁ መታተም ያለባቸውን የፌደራል መንግስት ህጎች በትርጓሜ አሊያም በዝርዝር አልለየም፡፡ ‘መመሪያ’ ከአዋጅና ደንብ ቀጥሎ አስገዳጅ ውጤት ያለው አንደኛው የፌደራል መንግስት ህግ እንደሆነ ክርክር አያስነሳም፡፡ ስለሆነም መመሪያዎች አለመታተማቸው የቆየ ልማድ እንጂ ህጉ በልዩ ሁኔታ ከህትመት ነጻ ስላደረጋቸው አይደለም፡፡

የአስተዳደር መ/ቤቶች በውክልና በተሰጣቸው ስልጣን የሚያወጡት አስተዳደራዊ ድንጋጌ በልዩ ሁኔታ ከህትመት ነጻ ባለመደረጉ የማሳተም ግዴታቸውን ሊወጡ ይገባል፡፡ ግዴታቸውን ካልተወጡ መመሪያዎቻቸው ውጤት ኖሯቸው ሊጸኑም አይገባም፡፡ ያልታተመ አዋጅና ደንብ ረቂቅ ሆኖ እንደሚቀር ሁሉ የመመሪያ ዕጣ ፈንታም ከዚህ አይለይም፡፡

የቋንቋ ጉዳይ

የገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን መመሪያዎች ከጥቂቶቹ በስተቀር አብዛኛዎቹ የተጻፉት በአማርኛ ቋንቋ ብቻ ነው፡፡ ባለስልጣኑ እንግሊዝኛውን ሲያስቀር ቋንቋውን አንብበው የማይረዱ በርካታ የውጭ አገር ባለሀብቶች ኢትዮጵያ ውስጥ እንዳሉ ዘንግቶታል ለማለት ይከብዳል፤ ችላ ብሎታል እንጂ፡፡ የዚህ የቆየ ልማድ ተገላቢጦሹን በኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ እናገኛለን፡፡ ባንኩ በመመሪያ አወጣጥ ሂደት አማርኛ አይጠቀመም፤ እንግሊዝኛ ብቻ እንጂ፡፡ ይህ የልማድ አሰራር በግልና በመንግስት ባንኮች የህግ አተገባበር መሰረታዊ ችግር ላይፈጥር ይችላል፡፡ ሆኖም በህግ ተርጓሚው ላይ የሚፈጥረው ችግር ቀላል ተብሎ የሚታለፍ አይደለም፡፡ እንግሊዝኛ የማወቅ ያለማወቅ አይደለም ቁምነገሩ፡፡

በእንግሊዝኛ ተረቆ የተዘጋጀ ህግ በአማርኛ ወይም በሌላ የክልል ቋንቋ ሲተገበር ውስብስብ ችግር ያስከትላል፡፡[4] በአንደኛው የሚገኝ ቃል በሌላኛው አይኖርም፡፡ አንደኛው በአግባቡ የገለጸውን ሀሳብ አንዳንዴ ሌላኛው ያዛባዋል፡፡ የፌደራል ነጋሪት ጋዜጣ በአማርኛና በእንግሊዝኛ እንዲታተም ያስገድዳል፡፡ በመካከላቸው የሚፈጠረውን የይዘት ልዩነት ለማስታረቅ አማርኛውን ብቻ ገዢ አድርጎ መጠቀም ውጤታማ አማራጭ ባይሆንም የአማርኛው የበላይነት ህጋዊ ዕውቅና አግኝቷል፡፡[5]

ከላይ ለመጠቆም እንደተሞከረው በነጋሪት ጋዜጣ መታተም ያለባቸው ሁሉም የፌደራል መንግስት ህጎች ናቸው፡፡ ሆኖም በተግባር ሲታይ መመሪያዎች ለብቻቸው አፈንግጠው አይታተሙም፡፡ ይህ እንደተጠበቀ ሆኖ የሚዘጋጁበት መንገድ በውክልና ስልጣን የሰጣቸው ህግ የያዘውን መልክና ቅርጽ ሊያንጸባርቁ ይገባል፡፡ የህግ አውጭነት ስልጣናቸው ምንጭ የሆነው የተወካዮች ምክር ቤት አዋጅ የሚጻፈው በአማርኛና በእንግሊዝኛ እስከሆነ ድረስ መመሪያዎችም ይህንኑ ተከትለው በሁለቱም ቋንቋዎች መዘጋጀት ይኖርባቸዋል፡፡ ከዚህ አንጻር በአንደኛው ቋንቋ ብቻ የተዘጋጀ መመሪያ አስገዳጅ ውጤት ሊኖረው አይገባም፡፡

የአስተዳደር መ/ቤቶች እየተከተሉት ያለው ዝብርቅርቅ የቋንቋ አጠቃቀም ከሚያስነሳው የህግ ጥያቄ በተጨማሪ ወደ አገራችን የሚመጡ የውጭ አገር ዜጎችና ባለሀብቶች የአገሪቱን ህግ አክብረው ለመንቀሳቀስና ለመስራት የሚያደርጉትን ጥረት ከማገዝ ይልቅ ተጨማሪ ጫና ይፈጥርባቸዋል፡፡ ሆኖም የቋንቋ ጉዳይ ለሰበር ችሎት ብዙም አሳሳቢ ሆኖ አለመገኘቱ ሲታይ የተለመደው አሰራር ከህግ አውጭው አዋጅ በስተቀር የዳኝነት አካሉ ፍርድ መቼም የሚያስተካክለው አይመስልም፡፡

በሰ/መ/ቁ. 43781[6] ብሔራዊ ባንክ በእንግሊዝኛ ቋንቋ ብቻ ያዘጋጀው መመሪያ በአማርኛ ተተርጉሞ ባለመገኘቱ በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ይግባኝ ሰሚ ችሎት ውጤት ቢነፈገውም የሰበር ችሎት፤

በመንግሥት አስፈጻሚ አካላት የሚወጡት የበታች ሕጎች… በተወሰነ ቋንቋዎች እንዲጻፉ የሚያስገድድ ሕግ የለንም፡፡

በሚል ምክንያት የመመሪያውን አስገዳጅነት ተቀብሎታል፡፡ ችሎቱ ‘ህግ የለም’ ይበል እንጂ ህጉስ አለ፡፡ የፌደራል ነጋሪት ጋዜጣ ማቋቋሚያ አዋጅ ቁ. 3/1987 መመሪያዎች እንዲታተሙ ከዚያም አልፎ በአማርኛና በእንግሊዝኛ ቋንቋዎች እንዲዘጋጁ ያስገድዳል፡፡ የአዋጁ ተፈጻሚነት በፌደራል መንግስቱ ህጎች ላይ እንጂ በተወካዮች ም/ቤት አዋጅ ላይ ብቻ አይደለም፡፡ ችሎቱ ‘መመሪያ በፌደራል መንግስት ህጎች ውስጥ አይጠቃለልም’ የሚል አቋም ከያዘ በመዝገቡ ላይ ‘መመሪያ ተላልፏል’ በሚል የወንጀል ክስ ቀርቦበት በይግባኝ ሰሚ ችሎቱ ነጻ የተደረገውን ተጠሪ በወንጀል ድርጊት ጥፋተኛ ሊለው ባልተገባ ነበር፡፡

[1] አመልካች ዳንዲቦሩ ዩኒቨርስቲ ኮሌጅ እና ተጠሪ እነ ተክሉ ኡርጋ ኢደኤ /2 ሰዎች/ ጥር 26 ቀን 2001 ዓ.ም. ቅጽ 8

[2] አመልካች ገ/ማሪም ገ/መድህን እና ተጠሪ ጣዕመ ወ/ስላሴ ሰኔ 21 ቀን 2005 ዓ.ም. ቅጽ 15

[3] የፌደራል ነጋሪት ጋዜጣ ማቋቋሚያ አዋጅ ቁ. 3/1987 አንቀጽ 2/2/

[4] የችግሮቹን መልክና ገፅታ በተለይ የተጠናቀሩት (Codified) ህጎቻችን በፈረንሳይኛና እንግሊዝኛ መረቀቃቸው ያስከትሉትን ችግር ለመረዳት Roger Briottet “French, English, Amharic: The Law in Ethiopia.” Mizan Law Review 3 (2): 331-340 (2009) ይመለከቷል፡፡

[5] አዋጅ ቁ. 3/1987 አንቀጽ 2/4/ ይመለከቷል፡፡

[6] አመልካች የኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን እና ተጠሪ አቶ ዳንኤል መኮንን ሐምሌ 14 ቀን 2002 ዓ.ም. ቅጽ 10

 

Nine Tips to Help You with Researching,Author: Library Social Media Team,November 23, 2017


dan-dimmock-323873

Do you want to be able to search efficiently and effectively? Below are nine tips and tricks to help you achieve better search results.

1. Analyse your assignment question
Keywords are key! You’ll need to analyse your assignment question to develop a list of keywords you can use in online search tools.

2. Brainstorm more keywords
Make sure you are using synonyms of your keywords. Consult a thesaurus; there are plenty of free versions online. Your topic is probably discussed by experts using a variety of terms and you’ll want to catch all of this research.

3. Watch out for words with different spelling options
You need to be aware of the words you are using which could have an alternative spelling. Remember, there are differences between British English and American English spelling i.e. colour and color. Some search tools will automatically find both spellings, but some you need to include both versions (see #7 for further tips).

4. Know your limits
Most search tools let you limit your results in a range of ways. Use these tools to focus your results to only the content you need.

5. Keep keywords together
Sometimes you really need your keywords to stick together. If the words aren’t in the correct order, then the results aren’t relevant. For example, higher education. Most search tools will find your phrase in the correct order if you enclose the words in quotation marks e.g. “higher education”.

6. Find multiple words in one go
Some search tools will only provide results for the exact keywords you use. For example, if you search for teen, it will only find results that contain teen. That’s fine, if that’s what you wanted. But chances are you would like results for teenteensteenager, and teenaged. If you use truncation, you don’t need to type in all of these words. Just use a symbol (usually the asterisk *) to tell the online search tool to find any endings to your keyword. For example, you can search for teen* and find results for all of them in one go.

7. Use wildcards
A wildcard is a symbol you can use in the middle of a word to catch any alternate spelling options for that word. The wildcard symbol varies between search tools, but is frequently a question mark (?) or an asterisk (*). For example, if you are searching for the keyword behaviour and know there is an alternative spelling option, you may search for behavio?r

8. Combine keywords with synonyms
Use Boolean operators to combine keywords and synonyms. Boolean operators are the terms AND, OR and NOT. Check out this YouTube video from Penfield Library to get an idea of how to use Boolean operators in your search.

9. Dig into references
Don’t forget to check the reference lists of the resources you find. They may list other helpful sources of information that you can use.

%d bloggers like this: